የእነእስክንድር ነጋ የመመረጥ መብት ተረጋገጠ


በሕግ ጥላ ስር የሚገኙት የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አመራር አባላት የሆኑት አቶ እስክንድር ነጋ፣ ወ/ሮ አስቴር ስዮም እና አቶ ስንታየሁ ቸኮል የመመረጥ መብታቸው ሊከብርላቸው እንደሚገባ የፌደራል ፍርድ ቤት ውሳኔ አስተላልፏል።
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ (National Electoral Board of Ethiopia- NEBE -የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ) ከሕግ አግባብ ውጭ እነእስክንድር ለምርጫ መወዳደር አይችሉም በማለት የመመረጥ መብታቸውን የከለከለ እና ፍርድ ቤት ቀርቦ ተከራክሮ የነበረ ሲሆን ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር አዳምጦ እና አስፈላጊ የሆኑ የሕግ አንቀጾችን መርምሮ እነእስክንድር ነጋ ምንም እንኳን በሕግ ጥላ ስር የሚገኙ ቢሆንም የአገሪቱ ሕግ ለምርጫ ከመወዳደር አይከላክላቸውም በማለት የመመረጥ መብታቸውን አረጋግጧል።
በቀጣይ ምርጫ ቦርድ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ያስፈጽም አያስፈጽም ተከታትለን የምናሳውቃችሁ ይሆናል። የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በአስተያየት መስጫ ሳጥናችን ውስጥ ያገኙታል።

Related posts

ከአውደ ውጊያ ወደ ሙሉ ድል እንዴት እንሸጋገር?

የጎንደር ጉዳይ!

ምርጫ 2013 | ምሉዕነት፣ ታማኝነት እና ግልጸኝነት